የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ
አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡ ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡
የሚሰጡ አገለግሎቶች
ወቅታዊ ዜናዎች
በግልም ሆነ በተቋም ደረጃ ለሚተገበሩ ስራዎች ውጤታማነት የዲጂታል ቴክኖሎጂ የሚኖረው አበርክቶ ከፍተኛ ነው: ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ። በክልሉ የ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ አፈጻጸም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ…
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ከ157ሺ በላይ ዜጎች የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማግኘታቸው ተመላከተ። በክልሉ የ 5 ሚሊየን ኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ኢኒሼቲቭ አፈጻጸም ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በወራቤ ከተማ እየተካሄደ ነው…
የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከክልሉ ጤና ቢሮ ጋር በጋራ የጨረራ አመንጪ መሣሪያዎችን ለምርመራና ህክምና አገልግሎት የሚጠቀሙ የጤና ተቋማትን ኢንስፔክሽን አደረገ፡፡ ወራቤ፣ የካቲት/2018 ዓ/ም ኢንስፔክሽኑ የተካሄደው በክልላችን በሰባት መዋቅር የሚገኙ…
ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማዘመን የተሻለ አገልግሎት መስጠትና ብልሹ አሠራርን በመከላከል የመንግስትን ሀብት ለመጠበቅ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተገለጸ። ተቋማትን በቴክኖሎጂ በማዘመን የተሻለ አገልግሎት መስጠትና ብልሹ አሠራርን በመከላከል የመንግስትን ሀብት…
የሳይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በሁሉም ዘርፍ የሚከናወኑ ተግባራት ብቁ እና ተወዳዳሪ የኢኮኖሚ ስርአት እንዲገነባ ልዩ ሚና እንዳለው ተገለጸ። የሳይንስ እና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎች በሁሉም ዘርፍ የሚከናወኑ የልማት ተግባራትን በማገዝ የአገልግሎት አሰጣጥን…
ተረጋገጡና ተዓማኒነት ያላቸው ክልላዊ መረጃዎችን በቀላሉ ማግኘት የሚያስችል የመረጃ ቋት ይፋ ተደረገ።የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ፕላን ልማት ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመሆን የለማ የተቀናጀ መረጃ ማሰራጫ ዌብ-ሳይት ርክብክብ ተደርጓል።…
ተልዕኮ
ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡
ራዕይ
“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”
እሴቶች
በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣
የስራ ፍቅርና ትጋት፣
ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
ለለውጥ በጋራ መስራት፤
ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
ችግር ፈቺነት፤
የማይረካ የመማር ጥማት፤
ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣