የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት

message

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ

                       አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት                  

የቢሮው ሀላፊ መልዕክት

ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ   ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው  አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡  ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው /ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡  ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ  በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ  መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት  የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው  ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡

ወቅታዊ ዜናዎች

Zenaa

3ኛው ዙር የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ውድድር፣ ዓውደ-ርዕይና የፓናል ውይይት እየተካሔደ ነው

" የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ ኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ"በሚል መሪ ሀሳብ የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ውድድርና የፓናል ውይይት በቡታጅራ ከተማ እየተካሔደ ነው

Zena1112

የተፈጥሮ ሃብትን ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ጋር ማጣመርና ማልማት ይገባል አለ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 3ኛው ዙር ክልል አቀፍ የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና የፈጠራ ስራዎች ውድድር አውደ ርዕይ እና የፓናል ውይይት እየተካሄደ ነው።

Zena1111

የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በአዳዲስ
ሃሳቦቻቸውና በፈጠራ ስራዎቻቸው የበቁ ወጣቶችን መፍጠር ተገቢ ነው:-ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ

Zena111

ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ 3ኛውን ዙር የሳይንስና ፈጠራ ሥራዎች ውድድርና ዓውደ-ርዕይ በቡታጅራ ከተማ መርቀው ለዕይታ ክፍት አደረጉ

Zena

‎ክልሉ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በሳይንስ፣በፈጠራ እና በቴክኖሎጂ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት እየተሰራ ነው :-ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ 

zena105

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)በስልጤ ዞን በወራቤ ከተማ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መርቀው ስራ አስጀመሩ።…

ተልዕኮ

ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡

ራዕይ

“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”      

እሴቶች

በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣

የስራ ፍቅርና ትጋት፣

ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣

ለለውጥ በጋራ መስራት፤

ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤

ችግር ፈቺነት፤

የማይረካ የመማር ጥማት፤

ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣

ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣