Skip to main content
zena113
የማህበራዊ ክላስተር የብልፅግና ህብረት እና የቤተሰብ መረጃዎችን ዲጂታላይዝ በሆነ መልኩ ለማደራጀት እና ለማስተዳደር የሚያስችል ሲስተም ለማልማት የሚያስችል ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ተገለፀ።
‎"ዲጂታላይዜሽን ለዘመናዊ አደረጃጀት፤ ጠንካራ አባላት ለተሻለ የፓርቲ ግንባታ!" በሚል መሪ ሀሳብ የመረጃ አደረጃጀትን ዲጂታላይዝ ለማድረግ ለክላስተሩ የብልጽግና ቤተሰብ አመራሮች የተዘጋጀ ስልጠናና የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሂዷል።
‎የማህበራዊ ክላስተር የብልፅግና ህብረት እና የቤተሰብ መረጃዎችን ዲጂታላይዝ በሆነ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችለው ሲስተም በክልሉ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ እንደሚለማ ተመላክቷል።
‎የስልጠና መድረኩን የመሩት የክልሉ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የወራቤ ክላስተር የብልፅግና ህብረት የአደረጃጀት ዘርፍ አመራር ወ/ሮ ነጅሚያ ራህመቶ እንዳሉት የፓርቲ አጠቃላይ መረጃዎችን ዘመናዊ በሆነ መልኩ ለማደራጀት የሚለማው ሲስተም ጠቃሜተው ከፍተኛ ነው።
‎ሲስተሙ መረጃን በተገቢው ከማደራጀት አንፃር ተያይዘው የሚነሱ ችግሮችን የሚቀርፍና በፍጥነትና ቀልጠፋ በሆነ አኳኃን መረጃን ዲጂታላይዝ አድርጎ በአግባቡ ለመሰነድ አጋዥ እንደሆነም ገልፀዋል።
‎"ከምርጫ መግስት ጠንካራ መንግስት" በሚል ሰፋፊ ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመላክተው ለዚህም ስኬታማነት በየዘርፉ እየተሰሩ የሚገኙ ስራዎች የመረጠንን ህዝብ እርካታ በሚያሳድግ አኳኃን መሆን አለበት ብለዋል።
‎እንደ መንግስትና ፓርቲ ለዲጂታላይዜሽን የተሰጠውን ትኩረት ለማሳካት በየደረጃው የሚሰሩ ስራዎችን ዲጂታላይዝ እንዲሆኑ ማድረግ ከሁሉም እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።
‎የማህበራዊ ክላስተር የብልፅግና ህብረት እና የቤተሰብ መረጃዎችን በአጭር ሰዓት ወደሚለማው ሲስተም ለማስገባት በትኩረት መስራት እንደሚገባም ወ/ሮ ነጅሚያ አሳስበዋል።
‎የክልሉ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሙህዲን ሁሴን በበኩላቸው በቢሮው የሚለማው ሲስተም በማኑዋል ይደራጅ የነበረን የመረጃ አደረጃጀት ወደ ዲጂታል የሚቀይር ወቅቱን የዋጀ ስራ ነው ብለዋል።
‎ቢሮው ለበርካታ ተቋማት እጅግ ጠቃሚ የሆኑ ሲስተሞችን እየለማ እንደሚገኝ ገልፀው ለማህበራዊ ክላስተር የብልፅግና ህብረት ቤተሰቦችን መረጃ በተደራጀ አግባብ ዲጂታላይዝ ለማድረግ የሚለማው ሲስተም የዚያው አካል ነው እንደሆነ ጠቁመዋል።
‎ሲስተሙ ሁሉንም መረጃዎችን በተሰናሰለ መልኩ የሚይዝ እና የህብረት ሰብሳቢው በሁሉም ቤተሰቦች እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን በቀላሉ እንዲቆጣጠሩ የሚያስችል እንደሆነም አቶ ሙህዲን ገልፀዋል።
‎አጠቃላይ ሲስተሙ የሚለማበትን ሂደት በተመለከተ እንዲሁም የቢሮውን የቤተሰብ ሲስተም ተሞክሮ የክልሉ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ባለሙያ አቶ ሞላልኝ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
‎የስልጠና መድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው የሚለማው ሲስተም አስፈላጊነቱና ጠቃሜተው ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል።
‎በስልጠናው የወራቤ ብልፅግና ፓርቲ ህብረት የስምንቱም ቤተሰብ አመራሮች እና ሲስተሙን የሚየለሙ ቡድኖች ተሳትፈዋል።