Skip to main content
zenaa 112
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ለክልሉ ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ አገልግሎት የሚያዘምን ሲስተም እንደሚለማ ተሠማ
‎ወራቤ ነሐሴ/2028 ዓ/ም
‎​በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የክልሉን ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን የሚያስችል አዲስ የዲጂታል ሲስተም ሊያለማ መሆኑ ተገለጸ።
‎​
‎ሲስተሙ ​ከልደት፣ ከጋብቻ፣ ከፍቺ እና ከሞት ምዝገባ ጋር የተያያዙ አገልግሎቶችን ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ለማድረግ ያለመ ነው።
‎​አሰራሩን ወደ ዲጂታል ማሸጋገር የህብረተሰቡን እንግልት ከማስቀረቱ ባሻገር የመረጃ ጥራትንና ደህንነትን አስተማማኝ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
‎​የቢሮው እንቅስቃሴ በክልሉ የመንግስት አገልግሎቶችን በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ በመደገፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ግቦችን ለማሳካት ከተያዙ እቅዶች አንዱ አካል መሆኑ ተመላክቷል።
‎በመድረኩ የተቋማቱ ኋላፊዎች; ሲስተም አልሚዎችና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል።