የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ
አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡ ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡
የሚሰጡ አገለግሎቶች
ወቅታዊ ዜናዎች

በዞን ደረጃ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን በማስጠገን ከ3 መቶ 5 ሺህ ብር በላይ የመንግስት ወጪ ማዳን መቻሉን የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ገለጸ። ግንቦት 15/2017 በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በኩል ከፍተኛ የሀርድዌር ጥገና ስልጠና ሲሰለጥኑ…

ብቃት ያለው እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ዜጋ ለመፍጠር በኢትዮ ኮደርስ የተገኘውን እድል መጠቀም እንደሚገባ ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አሳሰቡ። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) እንደገለጹት ብቃት ያለው እና በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ዜጋ ለመፍጠር…

ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያለንን ሙያዊ አቅም የሚያጎለብትና ክፍተቶቻችንን በመለየት በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንድንችል አጋዥ ነው - ሰልጣኞች። ስልጠናው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ያለንን ሙያዊ አቅም የሚያጎለብትና ክፍተቶቻችንን በመለየት በቀጣይ የተሻለ ስራ መስራት እንድንችል የሚያደርግ ነው ሲሉ ሰልጣኞች…

"የሀዲያ ዞንን የሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ማዕከል እናደርጋለን" - በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ 2ኛ ዙር ዞናዊ የምርምርና ፈጠራ ስራዎች ኤግዚብሽንና አውደ ርዕይ በሀዲያ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ፣ ትምህርት መምሪያ እና ሥራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዝ መምሪያ በጋራ የተዘጋጀ መድረክ…

ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ጉልህ ስኬቶች ተመዝግበዋል - ፕሬዚዳንት ታዬ። ባለፉት ዓመታት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ጉልህ ስኬቶች መመዝገባቸውን ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ። ፕሬዚዳንቱ ÷ በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን የቴክኖሎጂ ኤክስፖ…

በዞኑ የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎች በመደገፍና በማብቃት ለታለመላቸው አላማ እንዲውሉ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ አሳሰቡ። በጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ትምህርት መምሪያ በጋራ በመሆን "ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለሁለንተናዊ ሃገር…
ተልዕኮ
ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡
ራዕይ
“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”
እሴቶች
በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣
የስራ ፍቅርና ትጋት፣
ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
ለለውጥ በጋራ መስራት፤
ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
ችግር ፈቺነት፤
የማይረካ የመማር ጥማት፤
ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣