የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ
አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡ ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡
የሚሰጡ አገለግሎቶች
ወቅታዊ ዜናዎች

የህክምና መሳሪያዎች እና የመድሀኒት ስርጭት አስተዳደር ስርዓትን የሚያዘምን የመረጃ ቋት ሶፍት ዌር በማልማት ወደ ስራ መግባቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታወቀ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የመረጃ ቋት ሶፍት ዌር በማልማት ርክክብ ማድረጉን…

የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ በ2017 በጀት ዓመት ዓመታዊ የሴክተር ጉባዔ ለባለድርሻ አካላት ዕውቅና በመስጠት አበረታታ፡፡ በመድረኩ ቢሯችን ከተቋማት ጋር በፈጠረው ቅንጅታዊ አሰራር የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥ እንዲዘምን በማድረግ ረገድ ለክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ የነዳጅ መቆጣጠሪያ ሲስተም ልማት…

በየደረጃው የሚሰጠውን አገልግሎት ውጤታማ ለማድረግ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መጠቀም በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውሃ፥መስኖና ማዕድን ልማት ቢሮ አስታወቀ። ሀምሌ10/2017ቢሮው አሰራሩን ለማዘመን ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑም…

የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አገልግሎት በማዘመን የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እየሰራ ያለው ተግባር አበረታች መሆኑን ቋሚ ኮሚቴ ገለፀ። ሀምሌ 10/2017) የምክር ቤቱ የማህበራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮን የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል። የምክር…

የክልሉ የቱሪዝም ጸጋ በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ የታገዘ የቱሪዝም ስራ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ…

ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ። የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በትብብር ያለማው ድህረ ገጽ እና እለታዊ የነዳጅ መረጃ መመዝገቢያና መቆጣጠሪያ…
ተልዕኮ
ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡
ራዕይ
“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”
እሴቶች
በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣
የስራ ፍቅርና ትጋት፣
ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
ለለውጥ በጋራ መስራት፤
ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
ችግር ፈቺነት፤
የማይረካ የመማር ጥማት፤
ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣