የቢሮዉ ኃላፊ መልዕክት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ
አቶ ሰላሙ አመዶ ዋጨንጎ የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
የቢሮው ሀላፊ መልዕክት
ሳይንስና ኢንፎርመሽን ቴክኖሎጂ ለአንድ ሀገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማኀበራዊና ፖለቲካዊ ዕድገት የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከምንም በላይ መሆኑን ዛሬ ላይ የስልጣኔ ጫፍ የደረሱ፣ የበለፀጉና የዓለማችን ሃያላን ተብለው የሚጠሩ አገሮች ምሥክሮች ናቸው፡፡ ይህም በመሆኑ መንግስት የሀገራችን ሕዝብ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንዲሆንና የቴክኖሎጂው ሽግግር ከጫፍ እንዲደርስ ተግቶ በመሥራቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀላል የማይባል የሀገራችን ሕዝብ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ መሆን ችሏል፡፡ ለዚህም ማሳያ መሆን የሚችሉ በርካታ ተግባራትን መጥቀስ የሚቻል ሲሆን በክልላችን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከሚመለከታቸው መ/ቤቶች ጋር በመሆን በአያሌ የገጠር ቀበሌያትና ወረዳዎች የገጠሩ ሕብረተሰብ ከተለያዩ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች እንዲሁም ከሌሎች የመረጃ ምንጮች የሚፈልጓቸውን መረጃዎች በተለያዩ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎች አማካይነት ማግኘት እንዲችሉ የማህበረሰብ መረጃ ማዕከላትን አቋቁሞ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሽቦ አልባ ስልኮችም በብዙ የገጠር ቀበሌያት በቢሮውና አግባብነት ባላቸው ተቋማት በኩል የተሠራጩ ሲሆን እስኩል ኔትና ወረዳ ኔቶችም እንዲሁ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ እንዲሁም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልል ማዕከል፣ በዞኖች፤ በልዩ ወረዳዎች፤ በወረዳዎችና በከተማ አስተዳደሮች የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ደረጃ በደረጃ እየተዘረጋ ያለ ሲሆን በዋናነት የመንግስት መረጃ ሥርዓት የማሳለጥ፣ የቪዲዮ ኮንፍረንስ አገልግሎት በመስጠት ፈጣን የሆነ መረጃ እንዲዳረስ የማድረግና የማህበረሰብ መረጃና ሬድዮ አገልግሎት በመስጠት በርካታ ወጣቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን ወደ ስራ እያስገባ ይገኛል፡፡ ባለፉት ዓመታት በኢኮቴ ዘርፍ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመርቀው የሚወጡ ተመራቂዎችን በማህበር በማደራጀት የተለያዩ ድጋፎችን ማለትም ስልጠና፣ የገበያ ማፈላለግና የማማከር አገልግሎት በመስጠት የግል ካምፓኒ ፈጥረው ወደ ንግድ ዓለም እንዲገቡ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የቢሮውን ዌብ ሳይት በማልማት እና የፌስቡክ ገጽ በመክፈት እንዲሁም የተለያዩ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በተቋማችን አጠቃላይ አፈጻጸምና ሁኔታ ላይ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እተከናወነ ይገኛል፡፡
የሚሰጡ አገለግሎቶች
ወቅታዊ ዜናዎች
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከባለሙያዎችና ከሠራተኞች ጋር የ2018 በጀት ዓመት የ1ኛ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ።ታህሳስ 27/2018 ዓ/ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ፤ ችግር ፈቺ የምርምርና የቴክኖሎጂ ፈጠራ…
ታህሳስ 25/2018(ወልቂጤ) የኢትዮጵያ ባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የተሰራው ዘመናዊ የእንሰት ማዘጋጃ ቴክኖሎጂ ለወጣቶች የማሸጋገርና ማስተዋወቅ መርሀግብር በቸሃ ወረዳ የሰስየ ቀበሌ ተካሄደ። የጉራጌ ዞን ዋና…
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ እና የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የፈርኒቸር ኢንተርፕራይዞችን ለማጠናከር የምርምር ስምምነት ተፈራረሙ። ታህሳስ 20/2018 ዓ/ም የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ እና የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ዘላቂነት እና…
የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የ1ኛ ግማሽ ዓመት ስራዎች ክትትልና ድጋፍ ስራ ማድረግ ጀመረ። ወራቤ: ታህሳስ/2018 ዓ/ም የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በዞንና በልዩ ወረዳ ሳኢቴ መዋቅሮች የ2018_በጀት_ዓመት የ1ኛ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ክትትልና ድጋፍ የሚያደርግ ቡድን…
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት የብሄረሰቦች ምክር ቤት በክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ ቢሮ የለማዉን ዌብሳይት ተረከበ ። ምክር ቤቱ በክልሉ ህገመንግስት የተሰጠውን ተግባርና ሀላፊነት እንዲሁም ተቋሙ የምያከናዉናቸዉን ተግባራት መረጃ ለማሰራጨት ዌብሳይቱ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የምክርቤቱ ዋና አፈጉባኤ…
የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ከኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ባለስልጣን እንዲሁም ከክልሉ ጤና ቢሮ በጋር በቅንጅት የጨረራ አመንጪ መሣሪያዎችን ለምርመራና ህክምና አገልግሎት የሚጠቀሙ የጤና ተቋማትን ኢንስፔክሽን አደረገ፡፡ ወራቤ፣ ታህሳስ/2018 ዓ/ም ኢንስፔክሽኑ የተካሄደው በክልላችን በሚገኙ ዞኖች ካሉ የጤና…
ተልዕኮ
ለክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያደርጉ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በአግባቡ በማልማት፣ በመተግበርና በማስፋት ክልላዊ ብሎም አገራዊ የተወዳዳሪነት አቅምና በቴክኖሎጂ የዳበረ የአሰራር ስርዓት መፍጠር ነዉ፡፡
ራዕይ
“በ2030 በክልላችን ውጤታማ የሆኑ የሳይንስና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎችን በፍጥነት የመማር፣ የማልማት፤ የመፍጠር፣ የማላመድ እና የመጠቀም አቅም ተገንብቶ ማየት”
እሴቶች
በጎ ህሊናና ቅን ልቦና፣
የስራ ፍቅርና ትጋት፣
ያልተገደበ አስተሳሰብና ምናባዊ ጉዞ፣
ለለውጥ በጋራ መስራት፤
ውጤታችንም ሆነ ውድቀታችን የጋራችን ነው፤
ችግር ፈቺነት፤
የማይረካ የመማር ጥማት፤
ለትውልድ የሚተላለፍ መሠረት፣
ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርና ቀጣይነት ያለው መሻሻል፣