Skip to main content
aply

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሀላባ ዞን''የዘመነ ዲጂታል ኢኮኖሚ የዕድገታችን መሰረት ነው''በሚል መሪ ቃል የሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ከት/ት መምሪያ ጋር በመሆን የተዘጋጀ የፈጠራ ስራዎች ውድድር፣ባዛር፣ኤግዚቢሽን እና ፓናል ውይይት መድረክ እየተካሄደ ነው። መድረኩ በሀላባ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ በአቶ መሀመድ ሀሰን እና በአቶ አበበ አልዬ የሀላባ ዞን አስተዳደር ማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ እየተመራ ነው። በመድረኩ ላይም…

መሶብ የሁለተኛው ምዕራፍ የሀገር በቀል ሪፎርማችን አንዱ መሠረት ነው፡፡ የመንግስትን የመፈጸም አቅምን ለማሳደግ፣ ለማፋጠን ብሎም የተቋማት ግንባታን ለማጠናከር ማዕከሉ ትልቅ አቅምን ይፈጥራል፡፡ ለዓመታት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመፍታት በመንግስት በኩል ለሚደረገው ጥረትም ወሳኝ እርምጃ ነው። መሶብ ውብና ምቹ የሥራ ከባቢ፣ ሀገር በቀል የአገልግሎት ማሳለጫ የቴክኖሎጂ ስርዓትን ያሟላ እንዲሁም ሙያዊ እውቀትና ክህሎትን በተላበሱ ወጣት አገልጋዮች…

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ ዜጎቻችን ላይ ምሬት የሚፈጥሩ አሰራሮችን ፈትሾ ማስተካከል ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ ነው። ለዚህ ቁርጠኝነታቸን አንዱ ማሳያ የሆነውን የመሶብ የአንድ መስኮት አገልግሎት ማዕከልን ዛሬ መርቀናል። ይኽን አዲስ ማዕከል የሚገልጡ ሶስት ቁልፍ አላባውያን አሉ። የቆየ እና የተጎዳ ህንፃን ወደ ዘመናዊ እና ሥነውበታዊ ደረጃው ለሥራ ከባቢ አስደሳች ወደ ሆነ ህንፃ መለወጡ አንዱ ነው። አገልግሎቶችን…

በክልሉ ሁሉም ተቋማት ወረቀት አልባ አገልግሎት ለማቅረብ በሚያችላቸው ሲስተም ዝርጋታ ላይ ልዩ ትኩረት አድርጎ እየሰራ መሆኑን ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። (ሆሳዕና፣ ሚያዚያ 17/2017)፣ የቢሮው የ9 ወራት አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በዱራሜ ከተማ እየተካሄደ ነው። በክልሉ ሁሉም የመንግስት ተቋማት ከወረቀት ንክኪ ነጻ የሆነ አገልግሎት ለማቅረብ በሚያችላቸው የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሲስተም ዝርጋታ ላይ ልዩ ትኩረት አድርጎ እየሰራ…

የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኋላፊ አቶ ሠላሙ አማዶ ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ በዓል በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ ብለዋል፡፡ በዓሉ አንድነትን ይቅርታን ታናሽነትን መተሳሰብን ለወንድም እና እህትን በማገዝ የሚገለጽበት በመሆኑ በተለይ በህመም ላይ ያሉ ፣ ወላጆቻቸውን በተለያየ አጋጣሚ በህይወት ከጎናቸው የሌሉ፣ አቅመ…

ቢሮው ዲጂታል ቴክኖሎጂ በመጠቀም የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል በትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ ሳሙኤል ዳርጌ ገለጹ የማዕከላዊ ኢትዮጽያ ክልል ጤና ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የመድሃኒት እና የህክምና መሳሪያዎች ለመመዝገብ እና ለመቆጣጠር በለማ ሶፍት ዌር ግብዓት ለማሰባሰብ ውይይት ተካሂዷል ፡፡ በስጦታ አሊያም በግዢ የገቡ ንብረቶችን መመዝገብ ፣በባለሙያ ተፈትሾ ማሳለፍ ፣ የንብረቱን…

የፈጠራ ስራ ውድድርና ኤግዚቤሽን የእስካሁን አፈፃፀም አበረታች መሆኑ ተገለፀ። የፈጠራ ስራ ውድድርና ኤግዚቤሽን የእስካሁን አፈፃፀም አበረታች መሆኑን የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኋላፊ አቶ ሠላሙ አማዶ ገለጹ። ቢሯችን ከትምህርትና ከኢንተርፕራይዝና ስራ ዕድል ፈጠራ ሴክተሮች በጋራ በቅንጅት በማስፈፀሚያ ዕቅዱ መሠረት በት/ት ቤቶች; በወረዳ; በልዩ ወረዳ እና በዞን ደረጃ የፈጠራ ስራ ውድድርና ኤግዚቤሽን አፈፃፀም የተሻለ መሆኑን የቢሯችን ኋላፊ ገልጸው…

የሴቶች ልማት ህብረት መረጃን ዲጂታላይዝ በሆነ መልኩ ለማደራጀት የሚያስችል አዲስ ሲስተም ለምቶ ወደስራ እንዲገባ ከስምምነት ተደረሰ። ሲስተሙ የክልሉ ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ከክልሉ ሰይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አንዲሁም ከጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ጋር በመተባበር ያለመ ነው። በውይይቱ ንግግር ያደረጉት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሀመድናስር እንደገለፁት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ…

የጥንቃቄ መልዕክት ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች❗️ የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፣ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በቅርቡ በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች ለሀገራችን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካዉንቶችን በመንጠቅን ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አረጋግጧል። ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም…

ለኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ውጤታማነት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ!(መጋቢት 29/2017 ቡታጅራ) መንግስት ለሁሉም ዜጎች ለማድረስ ከአጋር አካላት ጋር በቅንጅት ያስጀመረውን የ 5 ሚሊዮን ሰልጣኞች ኢትዮ ኮደርስ ኢንሼቲቭ ስልጠና ውጤታማ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑን በመግለፅ ፤ የኢቲዮ ኮደርስ ስልጠና አስተባባሪ አብይ ኮሚቴው በ9 ወር ውስጥ የነበረውን የአፈፃፀም በጥልቀት ገምግሟል። የምስራቅ ጉራጌ ዞን…