Skip to main content
aply

የክልሉ የቱሪዝም ጸጋ በአግባቡ ለመጠቀም በቴክኖሎጂ የታገዘ የቱሪዝም ስራ ላይ በትኩረት እንደሚሰራ የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በጋራ በመሆን በጉራጌ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ የበለጸገው "የክልሉ የቱሪስት መስህቦች መረጃ ማስተዳደሪያ ሲስተም" እርክክብ ተደረገ። የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ ምክትል እና…

ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስርዓት መዘርጋት መቻሉን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አስታወቀ። የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ከክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በትብብር ያለማው ድህረ ገጽ እና እለታዊ የነዳጅ መረጃ መመዝገቢያና መቆጣጠሪያ ሲስተም የርክክብ መሮሐ ግብር ተካሂዷል። የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ አማካሪ አቶ መሐመድ ኑር ሳሊያ በርክክብ መርሐ ግብሩ…

የሳይንስ፣ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ባህል በማህበረሰቡ ውስጥ እንዲስፋፋ እየተሰራ ነወ።  የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለቴክኖሎጂ ሽግግር እና ለገበያ ማፈላለጊያ መንገድ አካባቢያዊ መፍትሄዎችን ማስፋፋት የሚችል ሀገራዊ የምርምርና ኢኖቬሽን ወርክሾፕና የጉብኝት መርሃ ግብር አካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ሃብት ልማት ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉ/ቋ/ኮ ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ነገሪ ሌኔጮ መንግስት የሀገራችንን ዜጎች ሁለንተናዊ ብልፅግና…

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በ2.8 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገዙ የተለያዩ እቃዎችን ድጋፍ አደረገ። ‎ ‎ድጋፉ እንተርኔት ኬብል፣ ሜንቴናንስ ቱልኪት፣ ድሪል ማሽን፣ የኮምፒዩተር አክስሰሪ፣ ኔትወርክ ቱልኪትን ጨምሮ የተለያዩ ለጥገና፣ለስልጠና፣ለእድሳት እና ለኢንኩቤሽን ማዕከል ማሻሻያ የሚዉል እቃዎችን ያካተተ ሲሆን በክልሉ ለሚገኙ ዞኖችና ልዩ ወዳዎች ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያዎችና ጽህፈት ቤቶች ተበርክቷል። ‎ ‎በረክክቡ…

በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና በውጤታማነት ተጠናክሮ ቀጥሏል።በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና በውጤታማነት ተጠናክሮ መቀጠሉን የክልሉ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ዜጎች በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ ዳታ ሳይንስና አርተሺሻል ኢንተለጀንሥ መሰረታዊ የዲጂታል ክህሎት እንዲኖራቸው ለማስቻል የኢትዮ ኮደርስ ሥልጠና በሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም ማስጀመራቸው ይታወሳል። በዚህም በርካታ…

የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይዎች ወጣቶች እርስ በርስ እንዲማማሩ ጠቃሚ ልምድ የሚፈጥሩ ናቸው ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፍቃዱ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይዎች ወጣቶች እርስ በርስ እንዲማማሩ ጠቃሚ ልምድ የሚፈጥሩ መሆናቸውን የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ ፍቃዱ ተናግረዋል ። በክልሉ ''ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ፣ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ…

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት 2ኛ ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ሰራዎች ዐውደ- ርዕይ እና ውድድር ተከፈተ። በክልሉ እየተካሄደ የሚገኘውን የሳይንስና ፈጠራ ስራዎች አውደ ርዕይ እና ውድድር የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አንተነህ ፈቃዱ እና አፈ ጉባኤ ፋጤ ሰርሞሎ በወልቂጤ ከተማ መርቀው ከፍተዋል። የማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር፣ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ አንተነህ…

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 2ኛ ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች ዐውደ_ርዕይ እና ውድድር ሰኔ 12 እና 13 በወልቂጤ ከተማ ይካሄዳል። "ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን የሳይንስ፣ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ማዕከል እናድርግ" በሚል መሪ ቃል ነው የሚካሄደው። 2ኛውን ዙር ክልላዊ የሳይንስና የፈጠራ ስራዎች ዐውደ_ርዕይ የክልሉ ትምህርት፣ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና የስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮዎች በትብብር አዘጋጅተውታል። ይህም ተማሪዎች፣…

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የአፍሪካ ህጻናት ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ በወራቤ ከተማ በህጻናት የተዘጋጀ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ተከፈተ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ዘቢባ መሐመድ ናስር እና የክልሉ ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ አውደ ርዕዩን ለእይታ ክፍት አድርገዋል። "የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድን ለማነጽ ህጻናት ተኮር ተግባራትን እናከናውን" በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ ክልላዊ ማጠቃለያ…

አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በመተግበርና በማስፋት ወቅቱን የሚመጥን ዲጂታል ተቋም ለመገንባት በትኩረት እየሰራ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው በዛሬው እለት በዲጂታል ሌተሪንግ ሲስተም አተገባበር ላይ በወራቤ ከተማ ለጠቅላላ ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል። ‎ ‎የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ሀላፊ አቶ ሰላሙ አማዶ በክልሉ በሚገኙ ተቋማት ቴክኖሎጂን በመተግበር፣በማለማመድና በማስፋት ወቅቱን…