Skip to main content
zena 113
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ የክረምት ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ስልጠና የመስክ ምልከታ ተካሄደ።
‎ነሐሴ; 2018 ዓ/ም ወራቤ
‎​በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት ለወጣቶች እያከናወነ የሚገኘውን የክረምት ስፔስ ሳይንስ; ጂኦስፓሻል; ኢንጂነሪንግና ሂሳብ ዙሪያ ስልጠና የክትትልና መስክ ምልከታ አካሄደ።
‎​ምልከታው በወራቤ ከተማ በሚገኘው የወራቤ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል የተካሄደ ሲሆን፣ ልዩ ተስጥኦ ያላቸው ተማሪዎች በስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል; ኢንጂነሪንግና ሂሳብ ዙሪያ ያገኙትን ሰፊ ተግባራዊ እውቀት ለመቃኘት ያለመ ነው።
‎በምልከታው ​የክረምት የበጎ ፍቃድ ስልጠናው ወጣቶች በዘመናዊው የጠፈርና ጂኦስፓሻል ቴክኖሎጂ ያላቸውን ክህሎት በማሳደግ ለወደፊት ፈጠራና ምርምር ዝግጁ እንዲሆኑ ያደርጋል ሲሉ የቢሮ ም/ኋላፊ የሆኑት አቶ ሙሂዲን ሁሴን መልዕክት አስተላልፈዋል።
‎​
‎አክለውም በክልሉ ቢሮ፣ በዞኑ መምሪያዎች እና በወራቤ ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል መካከል ያለው የተቀናጀ አሰራር ለስልጠናው ውጤታማነት ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል ብለዋል።
‎​በዚሁ የመስክ ምልከታ ፕሮግራም ላይ የቢሮ ኋላፊ አማካሪ አቶ ሁሴን ሳኒ; የሳይንስ ቴክኖሎጂ ዐቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አምደወርቅ ዘመዱ፣ የስልጤ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሹክራላህ አወል እንዲሁም የስልጤ ዞን ሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ጀሚላ ሁሴን የተገኙ ሲሆን፣ የነገዋን ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ለማበልፀግ የመስኩ ስልጠና ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።